የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) በሶዶ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ ምልከታ እያደረጉ ይገኛል ። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለፁት በፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች የሚሰለጥኑ ሰልጣኞች በሚወስዱት ስልጠና የህዝቡን ችግር መፍታት ይገባቸዋል ብለዋል።
የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የስራ ዕድል ፈጠራን ከስልጠና ጋር በማቀናጀት የውስጥ ገቢ አቅም ማሳደግ እንዳለባቸው የገለፁት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ጉብኝቱ ይህንኑ የሚያጠናክር ስለመሆኑ ጠቁመዋል ።
የሶዶ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን ኢንጂነር ያዕቆብ ያሲን በበኩላቸው ኮሌጁ የተለያዩ ስልጠናዎች በመስጠት ላይ ይገኛል ብለዋል። በስልጠናው አውቶሞቲቭ ፣ሆቴልና ቱሪዝም እንዲሁም አግሮ ፕሮሰሲንግ እንደሚካተቱ ኢንጂነር ያዕቆብ ጠቁመዋል ።
ኮሌጁን ዲጂታላይዝ ማዕከል ለማድረግ ዘርፈብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቁመው ፤በዚህም ከ90 ሚሊዮን ብር በላይ በሚሆን ወጭ የዳታ ማዕከል ስለመገንባቱ ተናግረዋል ። አሁን ላይ ኮሌጁ 1 ሺህ 944 ሰልጣኞችን ተቀብሎ በማሰልጠን ላይ ይገኛል ።


